● LivePolitics
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ በኢትዮጵያ ሰላምን ያደፈርሳሉ ባላቸው የህወሓት አመራሮች ላይ የቪዛ እገዳ ማድረጉን በይፋ አስታውቋል።
A
By Ashenafi
Jun 18, 20261 min read
780
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ በኢትዮጵያ ሰላምን ያደፈርሳሉ ባላቸው የህወሓት አመራሮች ላይ የቪዛ እገዳ ማድረጉን በይፋ አስታውቋል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሐሙስ ዕለት በኢትዮጵያ ሰላምን እያደናቀፉ ነው ያላቸውን ግለሰቦች ያነጣጠረ የቪዛ ገደብ መጣሉን አስታውቋል፤ ገደቡም በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሃት) ውስጥ ባሉ አቋማቸው ጠንካራ በሆኑ አመራሮች እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያተኮረ ነው። የሮይተርስ የዜና ዘገባ እንደሚያሳየው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ፥ "በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሃት) ጽንፈኛ አመራሮች እና በኢትዮጵያ መንግስት መካከል እየጨመረ የመጣው ውጥረት በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ድጋሚ የመቀስቀስ እንዲሁም በመላው ቀጠናው ያለውን ሰላምና ደህንነት የማናጋት ስጋት ደቅኗል" ብሏል።
አሜሪካ ከዚህ ቀደም በነበረው የትግራይ ጦርነት ወቅት (በ2013 ዓ.ም. / 2021) በተመሳሳይ ሁኔታ በሁለቱም ወገን (በመንግስትና በህወሓት) አመራሮች ላይ የቪዛ እገዳ ጥላ እንደነበር ይታወሳል። የዛሬው ውሳኔ ግን በቅርቡ በተፈጠሩት አዳዲስ ውጥረቶች ምክንያት በህወሓት አመራሮች ላይ የተደገመ እርምጃ ነው።
Filed under

