
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረበው አቤቱታ
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረበው አቤቱታ እና የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ! በምክክሩ ወቅት አዳዲስ ተሳታፊዎች ግልጽነት በጎደለው መንገድ እየተጨመሩ መሆኑን፣ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ከተመደቡበት ቡድን ውጭ በመግባት ተፅዕኖ እያሳደሩ እንደሚገኙ እና ሂደቱ ቀድሞ ወደተወሰነ የፖለቲካ አቅጣጫ እየተመራ ነው ሲል አብን ይከሳል። የባለሙያዎች ፓነል ገለልተኝነት የጎደለው መሆኑን እና የአንድን ወገን የፖለቲካ ትርክት ለማስረጽ እንደሚሞክርም የ አብን ደብዳቤ ይገልጻል።





